የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኢሰመኮ በአንዳንድ ፖሊስ ጣቢያዎች እድሜያቸው ከ18 በታች የሆኑ ተጠርጣሪዎች ለአካለ መጠን ከደረሱ ተጠርጣሪዎች ጋር ተቀላቅለው የሚታሰሩ መሆናቸውን ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ገልጿል
በሀገሪቱ በተከሰቱ ሰው ሠራሽ ቀውሶች እና የተፈጥሮ አደጋዎች ሳቢያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሴቶችና ሕፃናትን ለመፈናቀል፣ ለጾታዊ ጥቃቶች እና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች እንዲሁም ለሌሎች ተደራራቢ የመብት ጥሰቶች ተጋላጭነታቸውን እንደጨመረ በሪፖርቱ ገልጿል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን “በወንጀል የተጠረጠሩ ወይም የተከሰሱ ሕፃናት አያያዝ በማንኛውም ሁኔታ እና ወቅት ዓለም አቀፍና ሕገ መንግሥታዊ መስፈርቶችን በማሟላት እንዲተገበሩ” ጥሪ አቀረበ። ኮሚሽኑ “ከእስረኛ እናታቸው ጋር ማረሚያ ቤት ለሚቆዩ ሕፃናት አማራጭ የእንክብካቤ ማዕቀፍ” ሊመቻች እንደሚገባ ማሳሰቢያ ሰጥቷል
ይህ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀው የዘርፍ ሪፖርት ኢሰመኮ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ላይ በተጨማሪነት በተለይ የሴቶችና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ በዝርዝር በማተኮር ኮሚሽኑ የለያቸውን አበረታች እመርታዎችን፣ ዋና ዋና አሳሳቢ ጉዳዮችን እና ምክረ-ሐሳቦችን አካቷል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በሶማሌ ክልል የቆሎጂ መጠለያ ማዕከል ውስጥ በሚገኙ ተፈናቃዮች ላይ በተፈጸመ ጥቃት፣ ስድስት ሰዎች እንደተገደሉ አስታውቋል
በሶማሊ እና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢ፣ በሁለቱ ክልሎች የጸጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ የተኩስ ልውውጥ ምክንያት በአካባቢው የተጠለሉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና የአካባቢው ነዋሪዎች መጎዳታቸው አሳሳቢ መሆኑን ኮሚሽኑ ጠቅሷል
በኦሮሚያ እና በሶማሊ ክልል አዋሳኝ አካባቢ ላይ በክልሎቹ የጸጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ የተኩስ ልውውጥ ቢያንስ ስድስት ተፈናቃዮች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገልጿል
በሶማሊ እና ኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢ ላይ በክልሎቹ የጸጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ የተኩስ ልውውጥ፣ በሲቪል ሰዎች ላይ የደረሰውን ጉዳት ተገቢ የሆነ ምርመራ በማድረግ ለተጎጂዎች ዘላቂ መፍትሔ መስጠት ያስፈልጋል ሲል ኢሰመኮ አሳቧል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ‹‹በኦሮሚያ እና ሶማሊ ክልል የፀጥታ ሀይሎች መካከል በተካሄደ የተኩስ ልውውጥ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን›› መስከረም 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ባወጣውና ለአሻም በላከላት መግለጫ አመልክቷል
በተኩስ ልውውጡ ህይወታቸውን ያጡት ሰዎች በቆሎጂ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ እንደነበሩ ኮሚሽኑ ገልጿል