የአውሮፓ ኅብረት ልዑክ በኢትዮጵያ "ሹማን" የተባለውን ሽልማት ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢትዮጵያዊያን የመብት ተሟጋቾች ሸለመ። ሽልማቱ የተሰጠው ዴሞክራሲን፣ የሕግ የበላይነትን፣ ሰብአዊ መብቶችን፣ መቻቻልን እና እኩልነትን በማስፋፋት ረገድ የላቀ አስተዋጽዖ ያበረከቱ ለተባሉ ሰዎች ነው
በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት ልዑክ ቅጥር ግቢ በተካሄደ የአውሮፓ ኅብረት ሹማን ሽልማት (Schuman EU Awards) የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) ጨምሮ ከስድስት በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ሽልማቱን ማግኘት ችለዋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ እና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማእከል ዋና ዳይሬክተር ያሬድ ኃይለማርያምን ጨምሮ ስምንት የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ግለሰቦችና ተቋማት የአውሮፓ ኅብረት ሹማን ሽልማት ተበረከተላቸው
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በግል ስራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች መብት ዙሪያ ከሰጠኋቸው ምክረ ሃሳቦች አብዛኞቹ አልተተገበሩም አለ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት ልዑክ ቅጥር ግቢ በተካሄደ የሽልማት ሥነ ሥርዓት የአውሮፓ ኅብረት ሹማን ሽልማት (Schuman EU Awards) ተበርክቶላቸዋል
የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ ተባብሶ ቀጥሏል ተባለ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባለፉት ስድስት ወራት 161 ሲቪሎች መገደላቸውን ይፋ አደረገ። ለአማራ እና ለኦሮሚያ ክልሎች የግጭት ተሳታፊዎች የተኩስ አቁም ጥሪ አቀረበ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለይ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች በሲቪል ሰዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ተበራክተው መቀጠላቸውን አስታወቀ። ኮሚሽኑ መንግሥት በሁለቱ ክልሎች ከሚንቀሳቃሱ ታጣቂ ቡድኖች ጋር በሚያደርገው ውጊያ መካከል እንዲሁም ከውጊያ አውድ ውጪ በሚፈጸሙ ጥቃቶች በዜጎች ላይ ሞት እና ከፍተኛ የመብት ጥሰት እየደረሰ ነው ብሏል
በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በሶማሊ፣ በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ
የኦሞ ወንዝን በከፍተኛ ሁኔታ መሙላት እና የዳሰነች ወረዳ በርካታ አካባቢዎችን በጎርፍ መጥለቅለቅ ተከትሎ፣ ሰዎች ለመፈናቀል ከመዳረጋቸው ባሻገር፣ በሕይወታቸው፣ በአካላቸው፣ በንብረታቸው እንዲሁም ትምህርት እና ጤናን ጨምሮ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን በሚያገኙባቸው ተቋሟት ላይ ጉዳት የደረሰ መሆኑን የክትትል ሪፖርቱ ያመለክታል