Download
Download is available until [expire_date]
  • Version
  • Download 5
  • File Size 508.29 KB
  • File Count 1
  • Create Date December 25, 2023
  • Last Updated April 9, 2024

አንኳር ጉዳዮች:- የስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ የዘርፍ ሪፖርት

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከ2014 ዓ.ም. እስከ 2015 ዓ.ም. የበጀት ዓመት ድረስ ያለውን ጊዜ የሚሸፍን የመጀመሪያውን የስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ የተመለከተ ባለ 47 ገጽ የዘርፍ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ የመጀመሪያው የዘርፍ ሪፖርት ኢሰመኮ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ላይ በተጨማሪነት የስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች የሰብአዊ መብቶች አያያዝን በተመለከተ የለያቸውን መልካም ጅማሮዎች፣ አሳሳቢ ሁኔታዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን በዝርዝር አካቷል።

ኢሰመኮ በአፋር፣ በአማራ፣ በጋምቤላ እና በሶማሌ ክልሎች በሚገኙ የስደተኞች መጠለያ እና መቀበያ ጣቢያዎች ውስጥ ተጠልለው የሚገኙ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የከተማ ስደተኞችን ጨምሮ ከ650 ሺህ በላይ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን የሚያስጠልሉ 17 መጠለያዎችን፣ ሳይቶችን እና መቀበያ ጣቢያዎችን በመድረስ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ክትትሎች እና ምርመራዎችን በማካሄድ ሪፖርቱን አጠናቅሯል። ሪፖርቱ የስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ምዝገባ እና ሰነድ የማግኘት መብት፣ የጸጥታና ደኅንነት፣ ፍትሕ የማግኘት መብት፣ የመንቀሳቀስ መብት፣ የሰብአዊ ድጋፍ የማግኘት መብት እንዲሁም ለሕፃናት፣ ለሴቶች፣ ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኛ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች የሚደረግ ልዩ ድጋፍ እና በአጠቃላይ የዘላቂ መፍትሔዎች አተገባበር ላይ ትኩረት የሚያደርግ ነው።

የስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ የዘርፍ ሪፖርት