Download
Download is available until [expire_date]
  • Version
  • Download 104
  • File Size 36.00 KB
  • File Count 1
  • Create Date September 6, 2023
  • Last Updated November 27, 2023

የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጀውን የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ሁኔታ የተመለከተ ባለ 44 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ ዓመታዊ የዘርፍ ሪፖርት ኢሰመኮ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ላይ በተጨማሪነት በተለይ በአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ላይ በዝርዝር በማተኮር በበጀት ዓመቱ የታዩ መልካም እመርታዎች፣ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ አሳሳቢ ጉዳዮች እና ምክረ ሐሳቦችን ይዟል።

በሪፖርቱ ውስጥ የተካተቱት መረጃዎች እና ማስረጃዎች በዋናነት በኮሚሽኑ ከሐምሌ 2014 ዓ.ም. እስከ ሰኔ 2015 ዓ.ም. ካከናወኗቸው የሰብአዊ መብቶች ክትትል እና ምርመራ ሥራዎች፣ በግለሰቦች እና በሲቪክ ማኅበራት የቀረቡ አቤቱታዎች፣ መለስተኛ ጥናቶች እና በልዩ ልዩ የምክክር መድረኮች ላይ የተገኙ ግብአቶችን መሠረት ያደረጉ ናቸው። በተጨማሪም ከመንግሥት አስፈጻሚ አካላት፣ ከአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ማኅበራት አመራሮችና ኃላፊዎች ጋር ከተደረጉ ቃለመጠይቆች፣ ከመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እና ከሌሎች ሰነዶች የተገኙ መረጃዎች ተካትተዋል።

አንኳር ጉዳዮች:- የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት