የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለይ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች በሲቪል ሰዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ተበራክተው መቀጠላቸውን አስታወቀ። ኮሚሽኑ መንግሥት በሁለቱ ክልሎች ከሚንቀሳቃሱ ታጣቂ ቡድኖች ጋር በሚያደርገው ውጊያ መካከል እንዲሁም ከውጊያ አውድ ውጪ በሚፈጸሙ ጥቃቶች በዜጎች ላይ ሞት እና ከፍተኛ የመብት ጥሰት እየደረሰ ነው ብሏል
የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ለማሻሻል ፈጣን የሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያ እርምጃ ያስፈልጋል
Everyone shall have the right to freedom of association with others, including the right to form and join trade unions for the protection of his interests
ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በማኅበር የመደራጀት ነጻነት አለው፡፡ ይህም ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ የሠራተኛ ማኅበራትን የማቋቋም እና አባል የመሆን መብትን ይጨምራል
በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በሶማሊ፣ በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ
በግጭት ዐውድ ውስጥና ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችንና ሥጋቶችን በአስቸኳይ ማቆምና የአማራና ኦሮሚያ ክልሎችን ጨምሮ ሁሉንም የትጥቅ ግጭቶች በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምና የሰብአዊ መብቶች መከበርን ማረጋገጥ ይገባል
የኦሞ ወንዝን በከፍተኛ ሁኔታ መሙላት እና የዳሰነች ወረዳ በርካታ አካባቢዎችን በጎርፍ መጥለቅለቅ ተከትሎ፣ ሰዎች ለመፈናቀል ከመዳረጋቸው ባሻገር፣ በሕይወታቸው፣ በአካላቸው፣ በንብረታቸው እንዲሁም ትምህርት እና ጤናን ጨምሮ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን በሚያገኙባቸው ተቋሟት ላይ ጉዳት የደረሰ መሆኑን የክትትል ሪፖርቱ ያመለክታል
በተፈጥሮ እና ሰው ሠራሽ ምክንያቶች ለሚከሰቱ መፈናቀሎች የሰብአዊ መብቶች መርሖችን የተከተለ ዘላቂ መፍትሔ ማመቻቸት ይገባል
ረቡዕ ግንቦት 14 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በደቡብ ኦሞ ዞን፣ ዳሰነች ወረዳ በሚያዝያ ወር 2012 በወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት በኩል ምዝገባ የተደረገላቸው 62 ሺህ 790 ተፈናቃዮች ሲሆኑ በኅዳር ወር 2016 ዳግም በተደረገው ምዝገባ የተፈናቃዮች ቁጥር 79 ሺህ 828 ተፈናቃዮች እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ
A child temporarily or permanently deprived of his or her family environment, or in whose own best interests cannot be allowed to remain in that environment, shall be entitled to special protection and assistance provided by the State