3rd Edition Annual Human Rights Film Festival Report (December 2023) Since 2021, the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) has organized an annual human rights film festival to mark International Human Rights Day on December 10. By showcasing a diverse range of films, including short and full length features, documentaries, and fictional works, exploring various human...
ኢትዮጵያን ጨምሮ በአለማችን ግጭቶች በሚደረጉባቸው አከባቢዎች ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ለመቃወም በሚል የተጀመረው የፊልም ፌስቲባል ዘንድሮም ለሶስተኛ ጊዜ መደረጉን ጀምሯል
የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ እና የኢሰመጉ ምክትል ዋና ዲሬክተር አቶ ተስፋዬ ገመቹ በሰጡን አስተያየት፣ ለግጭቶች ብቸኛ መፍትሔ ነው ያሉት የድርድር አማራጭ፣ ተስፋ ሊቆረጥበት እንደማይገባ አመልክተዋል
ታኅሣሥ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው ዝግጅት የአጫጭር ፊልሞች እና የፎቶግራፍ ውድድር አሸናፊዎች ይፋ ተደርገዋል፣ ከታኅሣሥ 3 እስከ ታኅሣሥ 20 ቀን 2016 ዓ.ም. ባሉት ቀናት በአሶሳ፣ በጋምቤላ፣ በሃዋሳ፣ በጅማ፣ በጅግጅጋ፣ በመቀሌ እና በሰመራ ከተሞች በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይካሄዳል
በየዓመቱ ታኅሣሥ 10 የሚውለውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀን ለማሰብ የተጀመረው ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የዘንድሮው በሕይወት የመኖር መብት እና በቂ የሆነ መኖሪያ ቤት በማግኘት መብት ላይ ያተኮረ ነው
ኮሚሽኑ ከጥቅምት ወር መጨረሻ አንስቶ በክልሎቹ ውስጥ የተፈጸሙትን ጥቃቶች በተመለከተ የደረሱትን ጥቆማዎች እና አቤቱታዎችን መሠረት አድርጎ ባደረገው ክትትል፣ በሲቪል ሰዎች ላይ በተፈጸሙት ጥቃቶች ሳብያ መጠነ ሰፊ እና አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን አመልክቷል
የአካል ጉዳተኞች ቀንን ስናስብ ሊተገበሩ የሚችሉ ግቦችን በማስቀመጥ፣ የግቦቹን ውጤት ይፋ በማድረግ እንዲሁም የአካል ጉዳተኞችን መብቶች ለማስጠበቅ፣ ለማስፋፋት እና ለማስከበር የሚወሰዱ እርምጃዎችን ዘላቂነት በማረጋገጥ ሊሆን ይገባል
International Cooperation is essential to guarantee the rights of refugees, Internally Displaced Persons (IDPs) and Migrants
All entries in all categories will receive due recognition, and winners will be announced during the opening ceremony of the 3rd edition of the Annual Human Rights Film Festival
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው መግለጫ ሰሞኑን ባደረገው ክትትል በአማራ ክልል፣ በአዊ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር፣ በተፈጠረው ብሔር ተኮር ግጭት ሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱን እንዲሁም በኢንቨስትመንት ቦታዎች ላይ ጉዳት መድረሱን፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ ኢመደበኛ የአማራ ታጣቂዎች መሆናቸው የተገለጸ ያላቸው ቡድኖች በሰነዘሩት ብሔር ተኮር ጥቃት እና ይህንኑ ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት በርካታ በሚል በቁጥር ያልገለፃቸው ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት መድረሱን ገልጿል