የወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ሥርዓት የአካል ጉዳተኞችን እና የአረጋውያንን ሰብአዊ መብቶች እንዲያስከብርና ፍላጎቶቻቸውን እንዲያሟላ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ይጠይቃል
ተጠያቂነትን ለማስፈን፣ እውነትን ለማውጣት፣ ማኅበረሰባዊ እርቅ እና ፈውስ ለማምጣት እንዲሁም የተጎጂዎችን መፍትሔ የማግኘት መብትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ተግባራዊ መደረግ አለበት
All are entitled to equal protection against any discrimination in violation of this Declaration and against any incitement to such discrimination
ሰዎች ሁሉ በሕግ ፊት እኩል ናቸው፤ ያለምንም ልዩነት እኩል የሕግ ጥበቃ የማግኘት መብት አላቸው
ማእከላቱ የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መመዘኛዎች፣ የተ.መ.ድ. የአረጋውያን መርሆችና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወጣውን አነስተኛ መስፈርት በማሟላት የአገልግሎቶቻቸውን ጥራት ለማሻሻል እና ዘላቂነታቸውን ለማረጋገጥ መንግሥት ድጋፍ በማድረግ ግዴታውን ሊወጣ ይገባል
ክትትሉ በዋናነት ያተኮረው በማእከላቱ አደረጃጀት፣ በተጠቃሚዎች ልየታ ሥርዓት፣ በአገልግሎት ዓይነቶች እና በሰብአዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ ላይ ሲሆን፤ አግባብነት ካላቸው ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ሀገራዊ ሕጎች እና መርሆች አንጻር በመገምገም ምክረ ሐሳቦችን ይሰጣል፡፡ በዚህ ክፍል የክትትሉ አንኳር ጉዳዮች እና ምክረ ሐሳቦች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/ኮሚሽኑ) በሕግ ከተሰጡት ሥልጣን፣ ተግባርና ኃላፊነቶች መካከል የሰብአዊ መብቶች ክትትል ማድረግ አንዱ በመሆኑ በተለይ ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተጋላጭ የሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ያደረጉ የክትትል ሥራዎችን ያከናውናል፡፡ አረጋውያን ከዕድሜ መግፋት ጋር ተያይዘው ለሚመጡ አድሎዎች እና ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተጋላጭ በመሆናቸው እና የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ ለመስጠት ሲባል አረጋውያንን በአንድ ማእከል ውስጥ አሰባስቦ እንክብካቤ መስጠት...
ስምምነቱ “የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው የሲቪክ ማኅበራትን ጨምሮ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት በሕዝባዊ ምክክር የሚገኙ ግብአቶችን መሠረት አድርጎ እና መደበኛ ሀገራዊ የፖሊሲ አወጣጥ ሂደቶችን ተከትሎ ሊዘጋጅ እንደሚገባ” ያስቀምጣል
ምንም እንኳን ለተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግን በተመለከተ መንግሥት ተቀዳሚ ኃላፊነት ያለበት ቢሆንም የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም የዘላቂ መፍትሔ ጥረቶች ስኬታማ እንዲሆኑ የማገዝ ኃላፊነት አለባቸው
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከተከሰተው ችግር ጋር በተያያዘ ግድያዎች፣ እስሮች፣ መዋከቦች እና እንግልቶች መፈጸማቸውን ኢሰመኮ ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል