ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በቀለም፣ በዘር፣ በብሔር፣ በብሔረሰብ፣ በጾታ፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ ወይም በሌላ አመለካከት ወይም በሌላ አቋም ላይ የተመሠረተ ልዩነት ሳይደረግበት በማናቸውም የመንግሥት ደረጃ በየጊዜው በሚካሄድ ምርጫ የመምረጥ እና የመመረጥ መብት አለው
Every Ethiopian national, without any discrimination based on colour, race, nation, nationality, sex, language, religion, political or other opinion or other status, has the right to vote and to be elected at periodic elections to any office at any level of government
ኢሰመኮ በምርጫው ሂደት የሰብአዊ መብቶች ክትትል ያደርጋል
ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን እንዲሁም የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በስድስተኛው አጠቃላይ ምርጫ ከነበራቸው ተሳትፎ፣ ተደራሽነት እና አካታችነት አንጻር የተስተዋሉ ክፍተቶችን መለየት ለቀጠይ ምርጫ መሻሻል መሰረት ነው
በኮሚሽኑ የተለዩ ክፍተቶችን ለማስተካከል ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ጥረት ካላደረጉ በቀጣይ ምርጫዎች የዜጎች ሰብአዊ መብቶች በተለይም የመምረጥና የመመረጥ መብት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደራቸው እሙን ነው
ዶይቼ ቬለ በምርጫው በታዛቢነት ከተሳተፉት የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና የኢትየጶጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር (ኢሰመኮ) ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ትዝብታቸውን ተጋርቷል