ኮሚሽኑ እንደለጸው ሪፖርቱ ከመስከረም ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም. እስከ ታኅሣሥ 2017 ዓ.ም. አጋማሽ ባለው ጊዜ ውስጥ ያለውን ጊዜ የሚመለከት ነው ብሏል፡፡ ሪፖርቱ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በግጭት ዐውድ ውስጥ ባሉ አካባቢዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በሙሉ የሚሸፍን አይደለም ያለው ኮሚሽኑ በእነዚህ አካባቢዎች በነጻነት ተንቀሳቅሶ የተሟላ ክትትልና ምርመራ ለማካሄድ ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ፣ ውጤታማ ክትትልና ምርመራ የተከናወነባቸውን ጉዳዮች ብቻ በማሳያነት እንዳቀረበም ገልጿል
የዘፈቀደ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፣ አስገድዶ መሰወር፣ እገታ፣ በመዘዋወር መብትና በመጓጓዣ መንገዶች ላይ የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ገደብ፣ የሀገር ውስጥ መፈናቀል እና የዳኝነት ነጻነት መሸርሸሮች እንዳሉም ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ ጠቅሷል
ከአደባባይ በዓላትና ከዓለም አቀፋዊና አኅጉራዊ ስብሰባዎች ጋር በተያያዘ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በግዳጅ ወደ ማቆያ ማዕከል ማስገባትና ማቆየት ሊቆም ይገባል ሲል፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጠየቀ
በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ “ቃሊቲ አካባቢ” ተብሎ በሚጠራው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ባለ 'ሰፊ መጋዘን' ውስጥ፤ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች መኖራቸውንና ይህ ሰዎችን የመያዝና ወደ ማቆያ ማዕከል የማስገባት ድርጊት አሁንም መቀጠሉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታውቋል
የአካል ጉዳተኞችን አመራር ማሳደግ እና የመብቶቻቸውን መከበር ያለመ የሥዕል ዐውደ ርዕይ ተዘጋጀ
በአዲስ አበባ 90 በመቶ ሕንጻዎች ለአካል ጉዳተኞች አይሆኑም ተብሏል
“ካሉ አካል ጉዳተኛ ሕፃናት ውስጥ ከ85 እስከ 90 በመቶ የሚሆኑት የትምህርት እድል እያገኙ አይደለም” - ኢሰመኮ
በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚተላለፉ እገዳዎች የሲቪክ ምህዳሩን በማጥበብ በማህበር የመደራጀት መብት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ኮሚሽኑ አሳስቧል፡፡ ኢሰመኮ፤ ተቋሟቱ የፈጸሟቸውን ከባድ የሕግ ጥሰቶች በዝርዝር ባላስቀመጠ ደብዳቤ መታገዳቸው አሳሳቢ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ነው ያለው
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ፣ በሰብአዊ መብቶች ላይ ትኩረት ያደረገ የፊልም ፌስቲቫል በኢትዮጵያ ከተሞች በማካሄድ ላይ መኾኑን አስታውቋል
በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ሕፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች በግዳጅ የመከላከያ ሰራዊት አባል እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብሏል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን