ፍርድ ቤቶች ነጻ እና ገለልተኛ ካልሆኑ የሰብአዊ መብቶች ጥሰትን ጨምሮ ሌሎች ወንጀል ፈጻሚዎች ተጠያቂ ሳይሆኑ ሊቀሩ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ የሕግ የበላይነት እንዲሸረሸር እና ተጠያቂነት እንዳይረጋገጥ ያደርጋል ነው ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ
የጉዟቸው ዓላማም በዋናነት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኮምሽኑ ጋር በመተባበር ከግንቦት 12 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. የሚቆይ “የዳኝነት ነጻነት ለሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ያለው አንደምታ እና ተያያዥ ጉዳዮች …” ላይ ለፍርድ ቤቶች : ለፍትሕ ቢሮ: ለፖሊስና ሌሎች ለሚመለከታቸው ተቋማት ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች እና ለባለድርሻ አካላት በተዘጋጀው ወርክሾፕ ላይ ለመሳተፍ ሲሆን ዋና ኮሚሽነሩ እና ባልደረቦቻቸው ባሕር ዳር ሲገቡ የአማራ ብሔራዊ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ አለምአንተ አግደው እና ባልደረቦቻቸው ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል
የአዋጁን ውጤታማ አተገባበር ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት መሥራት አለባቸው
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎችን እና መርሖችን ያልተከተሉ እስሮች በአፋጣኝ እንዲቆሙ ጠየቀ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በትጥቅ ግጭት እና በጸጥታ መደፍረስ ወቅትም ቢሆን ሲቪል ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚያበቃ በቂ ሕጋዊ ምክንያት መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብሏል
ኢሰመኮ በዚህ መግለጫው፤ “ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ” እስር ተፈጽሞባቸዋል ካላቸው ውስጥ የመንግሥት ሠራተኞች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሚዲያ እና የሲቪክ ማህበረሰብ አባላት ይገኙባቸዋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል ከመስከረም ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ መልክ ጎንደር እና ባሕር ዳር ከተሞችን ጨምሮ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የሚፈጸመውን የበርካታ ሰዎች እስር በተመለከተ ክትትል ማድረጉን የሚቀጥል ሲሆን፣ በማናቸውም ወቅት ቢሆን የሚፈጸም እስር ተገቢውን የሕግ እና የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎች ሊከተል የሚገባ መሆኑን ያሳስባል
በትጥቅ ግጭት እና በጸጥታ መደፍረስ ወቅትም ቢሆን ሲቪል ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚያበቃ በቂ ሕጋዊ ምክንያት መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል
በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች በግጭት ተሳታፊ የሆኑ ሁሉም አካላት፤ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተኩስ አቁም በማድረግ ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሔ ለማፈላለግ በቁርጠኝነት እንዲሠሩ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በድጋሚ ጠይቋል
Participants held collaborative discussions on establishing a consortium for victims’ associations addressing key issues related to forming and operating the consortium, aiming to enhance collaboration and strengthen their role in the national transitional justice process