የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ በማረሚያ ቤቶች ላይ የሰብአዊ መብቶች አከባበር እና አጠባበቅ፤ የኑሮ ሁኔታ እንዲሁም ከቀለብ ጋር በተያያዘ በክትትል መምሪያ ዳይሮክተሬት በኩል በየጊዜው ክትትል ያደርጋል። በክትትል ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚበረታቱ ለውጦች ቢኖሩም ከቀለብ እና ከበጀት ጋር በተያያዘ ለሚነሱ ጥያቄዎች ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል ብለዋል
የሰብአዊ መብቶችን ባህል ለማድረግ ተተኪ ትውልድን በሰብአዊ መብቶች ዕውቀትና ክህሎት ማነጽ ይገባል
የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን የትምህርት መብት ለማረጋገጥ የትምህርት ግብአት አቅርቦት፣ ከባቢያዊ እና የመረጃ ተደራሽነት እንዲሁም የአመለካከት ክፍተቶች ላይ መሥራት ያስፈልጋል
ጥገኝነት የመጠየቅ መብት ማለት ምን ማለት ነው? ጥገኝነት የመጠየቅ መብት የሕግ መሠረቶች ምንድን ናቸው? የጥገኝነት ጠያቂዎች መብቶች ምንድን ናቸው? ኢትዮጵያ ውስጥ ጥገኝነት ለማግኘት የት ጥያቄ ማቅረብ ይቻላል? ኢትዮጵያ ውስጥ ጥገኝነት መጠየቅ ምን ሂደትን ያካትታል?
What Is Access To Asylum? What Are The Legal Bases For Access To Asylum? What Are The Rights Of Asylum Seekers? Where To Access Asylum In Ethiopia? What Process Does Asylum Seeking Entail In Ethiopia?
በሕክምና ተቋማት በመካሄድ ላይ ያሉ የሥራ ማቆም አድማዎች ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በር እንዳይከፍቱ ትኩረት ሊሰጣቸው እና ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል
ፍርድ ቤቶች ነጻ እና ገለልተኛ ካልሆኑ የሰብአዊ መብቶች ጥሰትን ጨምሮ ሌሎች ወንጀል ፈጻሚዎች ተጠያቂ ሳይሆኑ ሊቀሩ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ የሕግ የበላይነት እንዲሸረሸር እና ተጠያቂነት እንዳይረጋገጥ ያደርጋል ነው ያሉት ዋና ኮሚሽነሩ
States Parties shall take all appropriate measures to provide adequate, affordable and accessible health services, including information, education and communication programmes to women especially those in rural areas
አባል ሀገራት ለሴቶች በተለይም በገጠር ለሚገኙ የመረጃ፣ የትምህርት እና የግንኙነት መርኃ ግብሮችን ጨምሮ በቂ፣ ተመጣጣኝ እና ተደራሽ የጤና አገልግሎቶችን  ለመስጠት አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳሉ
የጉዟቸው ዓላማም በዋናነት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኮምሽኑ ጋር በመተባበር ከግንቦት 12 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. የሚቆይ “የዳኝነት ነጻነት ለሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ያለው አንደምታ እና ተያያዥ ጉዳዮች …” ላይ ለፍርድ ቤቶች : ለፍትሕ ቢሮ: ለፖሊስና ሌሎች ለሚመለከታቸው ተቋማት ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች እና ለባለድርሻ አካላት በተዘጋጀው ወርክሾፕ ላይ ለመሳተፍ ሲሆን ዋና ኮሚሽነሩ እና ባልደረቦቻቸው ባሕር ዳር ሲገቡ የአማራ ብሔራዊ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ አለምአንተ አግደው እና ባልደረቦቻቸው ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል