Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የጤና ተቋማት ሰዎችን አካል ጉዳተኝነትን መሰረት ካደረገ መድሎ የመከላከልና የመጠበቅ ኃላፊነት ሊወጡ ይገባል

April 19, 2022October 6, 2022 Public Statement

በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል በጤና ተቋም የተፈጸመ አካል ጉዳተኝነትን መሰረት ያደረገ መድሎ ምርመራ በማፋጠን ድርጊቱን የፈጸሙ ግለሰቦች በሕግ ሊጠየቁና ተበዳዮች ተገቢውን ፍትሕ እና ካሳ ሊያገኙ ይገባል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ይፋዊ መግለጫ

ሚያዚያ 11 ቀን 2014 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል፣ ጌዴኦ ዞን፣ ዲላ ዙሪያ ወረዳ በሚገኘው ጪጩ ጤና ጣቢያ በወ/ሮ ስምረት ጥላሁን ላይ ተፈጽሟል በተባለ አድሏዊ አያያዝ ሁኔታ ላይ በአካል ወደ ቦታው በመሄድ ከመጋቢት 16 እስከ መጋቢት 19 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ባደረገው ምርመራ፣ ወ/ሮ ስምረት ጥላሁን ዓይነስውር በመሆናቸው ያለባቸውን የአካል ጉዳት መሰረት ያደረገ አድልዎ በጤና ጣቢያው ባለሙያዎች የተፈጸመባቸው መሆኑን አረጋግጧል፡፡ 

የኢሰመኮ የአካል ጉዳተኝነትና የአረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር ርግበ ገብረሐዋርያ የምረመራውን መነሻ ሲያስረዱ፣ “በወ/ሮ ስምረት ጥላሁን ላይ የተፈጸመው ከአድልዎ ነጻ የመሆን መብት እንዲሁም የሕጻን ልጃቸውን ልዩ ጥበቃና እንክብካቤ የማግኘት መብት ጥሰት በአንድ ሰው እና አንድ ሕፃን ላይ የተፈጸመ ቢመስልም ምሳሌነቱ አካል ጉዳተኞችን ሁሉ የሚመለከት መሆኑን” አስታውሰዋል።

ኮሚሽኑ በምርመራው ከግል ተበዳይ፣ ከተበዳይ ቤተሰቦች፣ ከጤና ጣቢያው ባለሙያዎችና ኃላፊዎች፣ ከዲላ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ተወካይ፣ ከዲላ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም ከጌዲኦ ዞን አስተዳደር ጽሕፈት ቤት (ጽ/ቤት) ተወካዮች ጋር ካደረጋቸው ቃለ መጠይቆች እንዲሁም በጤና ጣቢያው በአካል ተገኝቶ ምልከታ በማድረግ ማስረጃዎችን አሰባስቧል፡፡  

ወ/ሮ ስምረት ጥላሁን በዲላ ከተማ፣ የሀሴ-ዴላ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ መጋቢት 6 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ በ 6፡30 ሰዓት አካባቢ የመውለጃ ጊዜያቸው በመድረሱ የቅድመ ወሊድ ክትትል ሲያደርጉበት ወደነበረበት የጪጩ ጤና ጣቢያ በመሄድ በዛው ዕለት ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ገደማ ልጃቸውን በሰላም ተገላግለዋል፡፡ በዕለቱ በጤና ጣቢያው የእናቶች ማዋለጃ ክፍል ውስጥ ተረኛ ሰራተኞች የነበሩ ነርሶች ተበዳይን ከሌሎች ሁለት ወላድ እናቶች ለይተው፣ ሰብአዊ ክብርን በሚነፍግ እና ለጤና  በማይመች መፀዳጃና መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ከተወለደው ሕፃን ልጃቸው ጋር ለሰዓታት እንዲቆዩ ማድረጋቸውን መረዳት ተችሏል፡፡ 

ወ/ሮ ስምረት፣ መፀዳጃ ክፍል ውስጥ እንዲተኙ ከተደረገ በኋላ በክፍሉ ውስጥ በነበረው መጥፎ ጠረን ምክንያት ከፍተኛ የሆነ የሆድ ቁርጠት እና የጤና መታወክ አጋጥሟቸዋል፡፡ የተበዳይ እህት የሆኑት ወ/ሪት መውደድ ጥላሁን ክፍሉ እንዲቀየርላቸው የጤና ጣቢያውን ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ቀና ምላሽ ባለማግኘታቸው ወ/ሮ ስምረት የተኙበትን ክፍል ፎቶ በማንሳት በማኅበራዊ ሚዲያ ለሕዝብ ይፋ አውጥተዋል፡፡ ፎቶው በማኅበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱ ከታወቀ በኋላ በወቅቱ ተረኛ ሰራተኞች የነበሩ ነርሶች ወ/ሮ ስምረትን ከነበሩበት መፀዳጃ ክፍል አውጥተው በጊዜው ወላድ እናቶች ያልነበሩበትና ተቆልፎ ወደነበረ ሌላ የድኅረ ወሊድ ማቆያ ክፍል እንዲዘዋወሩ ማድረጋቸውን ኢሰመኮ  ለመረዳት ችሏል፡፡ 

ወ/ሮ ስምረት በበኩላቸው ከወለዱ በኋላ እንዲያርፉ የተደረገበት ክፍል ውስጥ ያለው መጥፎ ጠረን ከየት የሚመጣ እንደሆነ በተደጋጋሚ ቤተሰባቸውን ይጠይቁ እንደነበረ፣ ቤተሰብ ግን ሁኔታውን ቢያውቁ ሊሰማቸው የሚችለውን ሥነልቦናዊ ጉዳት ከግምት በማስገባት ምላሽ እንዳልሰጧቸው ገልጸዋል። በቤተሰቡ እና በጤና ባለሙያዎቹ መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እየከረረ ሲመጣ ግን የትና በምን ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ለማወቅ እንደቻሉ ለኢሰመኮ አስረድተዋል።

ይህ ድርጊት መፈጸሙ ከተሰማ በኋላ የዲላ ወረዳ ዙሪያ አስተዳደር ጽ/ቤት ከወረዳው ፖሊስ እና ዓቃቤ ሕግ ጽ/ቤቶች የተውጣጣ የምርመራ ቡድን በማዋቀር ከመጋቢት 11 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ምርመራ እንዲጀመር ማድረጉን ገልጿል፡፡ በዚህም መሠረት፤ የዲላ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ድርጊቱ እንዲታረም አላደረጉም፣ መረጃም አዛብተዋል በሚል የጤና ጣቢያውን ኃላፊ ጨምሮ ወ/ሮ ስምረት ጥላሁን እና ሕጻን ልጇን በመፀዳጃ ክፍል ውስጥ እንዲተኙ አድርገዋል በሚል የተጠረጠሩ ሦስት የጤና ጣቢያውን ባለሙያዎች፤ በድምሩ አራት ሰዎች በቁጥጥር ሥር አውለው ምርመራ ማድረጉን ገልጿል፡፡ በምርመራው ሂደት በዲላ ዙሪያ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት (ፍ/ቤት) ከቀረቡ በኋላም በተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ በቁጥጥር ስር መቆየታቸውንና የዋስ መብታቸው የተከበረላቸው መጋቢት 22 ቀን 2014 ዓ.ም. መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።   

ከዚህ በተጨማሪ ድርጊቱን ተከትሎ ተገቢውን አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ አልወሰዱም ያላቸውን የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ እና ምክትል ኃላፊን ከሥራቸው እንዲታገዱ ማድረጋቸውን፣ “የግል ተበዳይን እና መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ ጠይቀው፣ ለወ/ሮ ስምረት ጥላሁን የሕጻናት አልባሳትና ምግብ-ነክ ስጦታዎችን” ማበርከታቸውን ገልጸዋል።በተጨማሪም ለወ/ሮ ስምረት የቀበሌ መኖሪያ ቤት በካሳ መልክ ለመስጠት እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸውን የዲላ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር እና የጌዲኦ ዞን አስተዳደር አካላት ለኮሚሽኑ አስታውቀዋል፡፡

ኮሚሽኑ በምርመራው ወ/ሮ ስምረት ጥላሁን ላይ ዓይነስውር በመሆናቸው ያለባቸውን የአካል ጉዳት መሰረት ያደረገ አድልዎ የተፈጸመባቸው ስለመሆኑ በምክንያታዊ ሁኔታ አሳማኝ ሆኖ አግኝቶታል፡፡  

ይኽም አካል ጉዳትንም ሆነ ሌሎች ሁኔታዎችን መሰረት ካደረገ ማንኛውም ዓይነት አድልዎ ነጻ የመሆን ሰብአዊ መብታቸውን የጣሰ ድርጊት ነው፡፡ የተበዳይ ሕጻን ልጅም በተወለደበት ወቅት ልዩ የጤና እንክብካቤና ትኩረት የሚያስፈልገው ሆኖ እያለ፤ ለጤና ፍጹም ተስማሚ ባልሆነ የመፀዳጃ ክፍል ውስጥ እንዲተኛ መደረጉ የሕፃኑን የሰብአዊ ክብር እና የልዩ ጥበቃና እንክብካቤ መብቶቹን የጣሰ ድርጊት ነው፡፡ 

ኮሚሽነር ርግበ ገብረሐዋርያ የጌዴኦ ዞን እና የዲላ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር አካላት የወሰዱትን ተገቢ ምላሾች አመስግነው፤ “የአጥፊዎችን ተጠያቂነት ለማረጋገጥ የግድ የተጠርጣሪዎችን መታሰር ሳያስፈልግ ተገቢው አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን እንዲከታተሉ፣ ተበዳዮች ተገቢውን ፍትሕ እና ካሳ ማግኘታቸውን እንዲያረጋግጡ” አሳስበዋል።

Related posts

February 16, 2022August 28, 2023 Human Rights Concept
ውሃ የማግኘት ሰብአዊ መብት
October 22, 2021August 28, 2023 Press Release
አዲስ አበባ፡ አቶ እስክንድር ነጋ ስለሚገኙበት ሁኔታ
September 9, 2022October 20, 2023 Press Release
ከትግራይ ክልልና ከአዋሳኝ የአማራ ክልል አካባቢዎች ተፈናቅለው በአዋሽ ሰባት የተያዙ ሰዎች የመንቀሳቀስ መብት በአፋጣኝ ሊከበር ይገባል
September 24, 2021September 26, 2021 EHRC Quote
ኦሮሚያ ክልል: ግድያ እና መፈናቀል በምስራቅ ወለጋ

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.