ኢሰመኮ ይህን የገለጸው በወቅቱ በጋምቤላ ከተማ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ መስከረም 18፤ 2014 ይፋ ባደረገው የምርመራ ሪፖርት ነው። ኮሚሽኑ በዚሁ ሪፖርቱ፤ ሰኔ 7፤ 2014 በጋምቤላ ከተማ የተደረገውን ውጊያ ተከትሎ፤ ኢሰመኮ አንድ ወር ለሚጠጋ ጊዜ ምርመራ ሲያደርግ እንደነበር አስታውቋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጋምቤላ ከተማ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች፣ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሸኔ) እና በጋምቤላ ነጻነት ግንባር (ጋነግ) መካከል የተደረገው ውጊያን ተከትሎ ከሰኔ 7 እስከ 9 ቀን 2014 ዓ.ም. በክልሉ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ታጣቂ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ግድያዎችን፣ የአካል ጉዳቶችን፣ የንብረት ጉዳት...
በጋምቤላ ከተማ ሰኔ 07/2014 ዓ.ም በክልሉ የፀጥታ ኃይሎች፣ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እና በጋምቤላ ነጻነት ግንባር የተደረገውን ውጊያ ተከትሎ ቢያንስ 50 ሰላማዊ ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሸን (ኢሰመኮ) አስታወቀ
በድርጊቱ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ታጣቂ ቡድን፣ የጋምቤላ ነጻነት ግንባር ታጣቂ ቡድን፣ የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይሎች፣ ፖሊሶች፣ ሚሊሻዎች እና ተባባሪ ወጣቶች ተሳትፈዋል፤ ድርጊቱን ሲመሩ እና ሲያስፈጽሙ የነበሩ ኃላፊዎችም ነበሩ
በኦሮምያ ክልል፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች በሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በተፈጸሙ ጥቃቶች ከ100 በላይ ሲቪል ሰዎች ተገለዋል ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ
ጥቃቱ “በኦነግ ሸኔ፣ በአማራ ኢመደበኛ ታጣቂ ኃይሎችና ግለሰቦች በተከታታይ መፈጸሙን” ኢሰመኮ አስታውቋል
መንግሥት የሲቪል ሰዎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ግዴታውን በአግባቡ መወጣት ይኖርበታል
EHRC reiterates its readiness to cooperate with the ICHREE within the framework of cooperation proposed, including support to the ICHREE on discussions with the State to grant access to affected areas in Northern Ethiopia
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና የተባበሩት መንግሥታት ባለፈው ዓመት ባደረጉት ጣምራ ምርመራበትግራይ ክልል ውስጥ በነበረው ጦርነት በሰብዓዊነት ላይ የተፈፀመ እና የጦር ወንጀል ሊባሉ የሚችሉ የወንጀል ዓይነቶች መፈፀማቸውን የሚያመለክቱ ማስረጃዎች መገኘታቸውን አመልክተው ነበር
ከሌሎች የተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች በተለየ መልኩ ከሕግ አግባብ ውጪ እና የመንቀሳቀስ መብታቸው ተነፍጎ፣ የሰብአዊ ድጋፍ በበቂ ሁኔታ ሳይቀርብላቸው በጃሬ መጠለያ ጣቢያ ለበርካታ ወራት ተይዘው የቆዩ ናቸው ያለው ኮሚሽኑ ተፈናቃዮቹ የሚገኙበትን ሁኔታ ለመመልከት ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም ከመንግሥት አካላት አፋጣኝ ምላሽ አለማግኘቱን ተናግሯል