ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በአዋጅ ቁጥር 676/2002 ተቀብላ አጽድቃለች። ይህንን ስምምነት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ለመተርጎምና ለማሰራጨት በአዋጅ ቁጥር 210/1992 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) አንቀጽ 6(8) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ወደ አማርኛ ቋንቋ አስተርጉሞ አሳትሟል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰዎችና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር የአረጋውያን መብቶች ፕሮቶኮል በአዋጅ ቁጥር 1182/2012ተቀብላ አጽድቃለች። ይህንን ፕሮቶኮል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ለመተርጎምና ለማሰራጨት በአዋጅ ቁጥር 210/1992 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) አንቀጽ 6(8) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ወደ አማርኛ ቋንቋ አስተርጉሞ አሳትሟል።
This Executive Summary consolidates the key findings and issues of concern identified in the 4th Annual Ethiopia Human Rights Situation Report of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC), covering the fiscal year from June 2024 to June 2025 Click here for the Amharic version (በአማርኛ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ) Click here for the full report (Amharic)
ከሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍነውና ለአራተኛ በጀት ዓመት በዚህ መልኩ ተጠናቅሮ ይፋ የተደረገው ይህ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዓመታዊ ሪፖርት ኮሚሽኑ ባደራጃቸው ልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች እና የከተማ ጽሕፈት ቤቶች አማካኝነት በተሰበሰበ መረጃ መሠረት ሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን ጠቅለል ባለ መልኩ የሚዳስስ ነው። የሪፖርቱ አንኳር ጉዳዮች Executive...
ሁሉንም የማኅበረሰብ ክፍሎች በእኩልነት የሚያሳትፍ እና አካታች የሀገራዊ ምክክር፤ በሰብአዊ መብቶች መርሖች ላይ የተመሠረተ እና ተጎጂዎችን ማእከል ያደረገ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ትግበራን ማረጋገጥ ይገባል
ከሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍነውና ለአራተኛ በጀት ዓመት ይፋ የተደረገው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዓመታዊ ሪፖርት ያካተታቸው አንኳር ጉዳዮች በእንግሊዝኛ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ (Click here for the English version) ሙሉ ሪፖርቱ እዚህ ተያይዟል
በሰብአዊ መብቶች ላይ በጋራ መምከር እና አጋርነትን ማጠናከር ለሰብአዊ መብቶች መስፋፋት፣ መከበር እና ጥበቃ ጉልህ ሚና አለው
ኮሚሽነሮቹ በሰጡት አመራር የኢሰመኮን ሥራ በማጠናከር፣ ተደራሽነቱን በማስፋት እና በሕዝብ እንዲሁም በዓለም አቀፍ አጋሮች ዘንድ መተማመንን በማሳደግ ረገድ የሚጠበቅባቸውን ሚና አበርክተዋል
አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሚገጥሟቸውን ተደራራቢ ተግዳሮቶች በመቅረፍ የትምህርት መብታቸውን ማረጋገጥ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃል
ማንኛውም አካል ጉዳተኛ ሰው ዘርን፣ ጎሳን፣ የቆዳ ቀለምን፣ ጾታን፣ ቋንቋን፣ ሃይማኖትን፣ ፖለቲካን ወይም በሌላ ዐይነት አመለካከት፣ በብሔራዊ ወይም ማኅበራዊ መሠረትን፣ ሃብትን፣ ትውልድን ወይም ሌላ ሁኔታን ጨምሮ በማንኛውም ምክንያት ማንኛውም ዐይነት ልዩነት ሳይደረግበት በዚህ ፕሮቶኮል ውስጥ ዕውቅናና ዋስትና የተሰጣቸው መብቶች እና ነጻነቶችን የማግኘት እና የመጠቀም መብት አለው